
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
“ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ፣ ለፍጥረትም ሁሉ ወንጌልን ስበኩ።” ማር ፲፮፤፲፭
እንኳን ወደ ቤተ ክርስቲያናችን ድረ ገጽ በሰላም መጡ።
የርዕሰ አድባረት ደብረ ሰላም ቅድስት ማርያም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰሜን አሜሪካ ዋና ከተማ መሐል ላይ ከስልሳ ሽህ ሰኩየር ጫማ በላይ ይዞታ ገዝታ ላላፉት ሃያ ዓመታት መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎቷን እያከናወነች የምትገኝ ቤተ ክርሰቲያን ናት።
ቤተ ክርሰቲያናችን ከጊዜ ወደ ጊዜ በምታሳየው ለውጥ እነሆ ዛሬ በካህናትና በምዕመናን ብዛት እንዲሁም በመንፈሳዊና በማህበራዊ አገልግሎተች ስፋት በሰሜን አሜሪካ ውስጥ ከሚገኙት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርሰቲያናት ውስጥ በግንባር ቀደምትነት የምትጠቀስ ቤተ ክርሰቲያን ለመሆን በቅታለች።
ቤተ ክርስቲያናችን ምዕመናን ወደ ቤተ ክርስቲያን መጥተው እረፍት እንዲያገኙና ክካህናት የምክር አገልግሎት እንዲያገኙ ሳምንቱን ሙሉ በሯ ክፍት የሆነች፣ ሥርዓተ ቅዳሴው፣ ማኅሌቱ፣ ሰዓታቱ እና ሌሎችም አገልግሎቶች ሳይቋረጡ ከዓመት እስከ ዓመት የሚከናወንባት ቤተ ክርሰቲያን ናት።
ቤተ ክርስቲያናችን በእግዚአብሔር እርዳታ፣ በእመቤታችን አማላጅነት እንዲሁም በካህናትና በምዕመናን ጸሎት፤ በመንፈሳዊና በማህበራዊ አገልግሎት፣ በካህናትና በምዕመናን ቁጥር፣ በንብረትና በሀብት ብዛት አሁን ለደረሰችበት ደረጃ ደርሳለች። አሁንም ኢትዮጵያንና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ምንነት ለምዕራቡ ዓለም የሚያሳይ ታሪካዊ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ለመገንባት ጉዞ ጀምራለች።
(Amharic Font download)
አሁንም፥ እነሆ፥ እግዚአብሔር ለመቅደስ የሚሆን ቤትን ትሠራ ዘንድ መርጦሃልና ጠንክረህ ፈጽመው።
መጽሐፈ ዜና መዋዕል ቀዳማዊ 28 :10
Please support the new Church Construction (Pledge Form, የቃል፡ መግቢያ፡ ቅጽ። ) |
|
Featured News, Reports & Updates
|
|
|
|
|
What's New
Press Release: (መግለጫ)
በርዕሰ፡አድባራት ደብረ፡ሰላም ቅድስት ማርያም ቤተ፡ክርስቲያን እና ከደብረ፡ሰላም ቅድስት ማርያም የመረዳጃ እድር መሀል በተደረገዉ እርቀ ሰላም ከሁለቱም ወገን የተሠጠው መግለጫ ::
|
|
Administration Documents
Finacial Documents
Report / News
|



