
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
“ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ፣ ለፍጥረትም ሁሉ ወንጌልን ስበኩ።” ማር ፲፮፤፲፭
እንኳን ወደ ቤተ ክርስቲያናችን ድረ ገጽ በሰላም መጡ።
የርዕሰ አድባረት ደብረ ሰላም ቅድስት ማርያም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰሜን አሜሪካ ዋና ከተማ መሐል ላይ ከስልሳ ሽህ ሰኩየር ጫማ በላይ ይዞታ ገዝታ ላላፉት ሃያ ዓመታት መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎቷን እያከናወነች የምትገኝ ቤተ ክርሰቲያን ናት።
ቤተ ክርሰቲያናችን ከጊዜ ወደ ጊዜ በምታሳየው ለውጥ እነሆ ዛሬ በካህናትና በምዕመናን ብዛት እንዲሁም በመንፈሳዊና በማህበራዊ አገልግሎተች ስፋት በሰሜን አሜሪካ ውስጥ ከሚገኙት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርሰቲያናት ውስጥ በግንባር ቀደምትነት የምትጠቀስ ቤተ ክርሰቲያን ለመሆን በቅታለች።
ቤተ ክርስቲያናችን ምዕመናን ወደ ቤተ ክርስቲያን መጥተው እረፍት እንዲያገኙና ክካህናት የምክር አገልግሎት እንዲያገኙ ሳምንቱን ሙሉ በሯ ክፍት የሆነች፣ ሥርዓተ ቅዳሴው፣ ማኅሌቱ፣ ሰዓታቱ እና ሌሎችም አገልግሎቶች ሳይቋረጡ ከዓመት እስከ ዓመት የሚከናወንባት ቤተ ክርሰቲያን ናት።
ቤተ ክርስቲያናችን በእግዚአብሔር እርዳታ፣ በእመቤታችን አማላጅነት እንዲሁም በካህናትና በምዕመናን ጸሎት፤ በመንፈሳዊና በማህበራዊ አገልግሎት፣ በካህናትና በምዕመናን ቁጥር፣ በንብረትና በሀብት ብዛት አሁን ለደረሰችበት ደረጃ ደርሳለች። አሁንም ኢትዮጵያንና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ምንነት ለምዕራቡ ዓለም የሚያሳይ ታሪካዊ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ለመገንባት ጉዞ ጀምራለች።
|
ስብከተ ወንጌል: ዘወትር ረቡዕ እና ዓርብ ከምሽቱ 12፡30 (6:30pm)ጀምሮ
የቅዳሴ አገልግሎት: ዘወትር እሁድ ከጧቱ 12፡00 (6:00am) ጀምሮበ21 - የእመቤታቸን ወርሃዊ በዓልበ24 - የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ወርሃዊ በዓል የነግህ ጸሎት (የኪዳን ጸሎት): ከልደታ እስከ ሥላሴ ከጧቱ 11 ሰዓት (5:Am) ጀምሮ
የሰንበት ትምህርት ቤት መርሐ ግብር:ዘወትር እሁድ ከቀኑ 6፡00 – 9፡00 ሰዓት (12:00pm – 3:00pm) ቤተ ክርስቲያኒቱ ክፍት የምትሆንባቸው ሰዓታት ለጸሎትና ካህናትን ለማነጋገር ለሚመጡ ምዕመናን: ቤተ ክርስቲያናችን ቀኑን ሙሉ ክፍት ናት። |
|
|
|---|
|
Featured News & Updates
|
|
Upcoming Events
|
|
|
>>
|
|
|
|
|
>>
|
|||
|
>>
|
|||
|
>>
|
|
||

